![](https://benchshekozonecom.gov.et/wp-content/uploads/2023/08/1693316642477.jpg)
ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው የደቡብ ቤንች ወረዳ ም/ቤት 5ኛ ዙር 33ኛ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ የወረዳውን የካብኔ አባላት ሹመት በማፅደቅ ተጠናቅቋል ።
![](https://benchshekozonecom.gov.et/wp-content/uploads/2023/08/1693316632137.jpg)
በሁለት ቀናት የጉባኤው ቆይታም ም/ቤቱ የአስፈጻሚዎችን፣ የፍ/ቤቱን እና የምክር ቤቱን
የ2015ዓ.ም ሪፖርት እና የ2016ዓ.ም እቅድ ገምግሞ አጽድቋል ።
ምክር ቤቱ የወረዳውን ካቢኔ ሹመት ፕሮፖዛል በወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ወልዱ ባጪ አማካይነት ቀርቦ ም/ቤቱ የካቢኔ አባላት ላይ አስተያየት ከሰጠበት በኋሏ አፅድቋል በዚሁ መሰረት:-
1ኛ. አቶ ብርሃኑ ተስፋዬ የደቡብ ቤንች ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ሀላፊ
2ኛ.አቶ ወንድሙ ሰውነት ሰላም ፣ጸጥታና ሚሊሻ ጽ/ቤት ሀላፊ
3ኛ.ወ/ሮ ሸዋዬ ጉደማ የሴቶች፣ህጻናት ፣ወጣቶችና ጽ/ቤት ሀላፊ
4ኛ.ወ/ሪት ታደለች ጋይድ ፐብሊክ የሰርቪስ ጽ/ቤት ሀላፊ
5ኛ.አቶ ዳንኤል ዘለቀ ንግድ ፣ክህሎትእና ኢንተርፕራይዝ ጽ/ቤት ሀላፊ
6ኛ.አቶ በረከት አይበራ በህል፣ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ሀላፊ
7ኛ.አቶ ዳንኤል ወዳጆ የከተማ እና ቤቶች ልማት ጽ/ቤት ሀላፊእንዲሆኑ ም/ቤቱ በሙሉ ድምጽ ያጸደቀ ሲሆን የካቢኔ አባላቱም ቃለ-መሀላ ፈጽመዋል።
![](https://benchshekozonecom.gov.et/wp-content/uploads/2023/08/1693316645354.jpg)
ምክር ቤቱም በተጨማሪ የወረዳውን የ2016ዓ.ም በጀት 339 ሚሊዮን 483 ሺ2 መቶ5 ብር ማፅደቁን ከወረዳው መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።